አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ሀላፊዎች ጋር ውይይት አደረገ።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርዱ በሸዋሮቢት፣ በጎንደር፣ በኮምቦልቻ እና በባህር ዳር በወንጀል ተጠርጥረው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ በህግ ጥላ ስር ያዋሉትን ተጠርጣሪዎች በጎበኘበት ወቅት ተጠርጣሪዎቹ ባነሷቸው ሀሳቦች ዙርያ ቦርዱ ምክረ ሀሳብ ለእዙ በማቅረብ ውይይት አድርገዋል።