Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢራናዊቷ ናርጌስ ሞሐመዲ የ2023 የኖቤል የሰላም ሽልማትን አሸነፈች

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 25 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023 የኖቤል የሰላም ሽልማት ኢራናዊቷ ናርጌስ ሞሐመዲ አሸነፈች።
ናርጌስ ሞሐመዲ በሀገሯ ኢራን በሚገኘው ኤቪን በሚባለው ማረሚያ ቤት በእስር ላይ ትገኛለች።
ወጣቷ በሀገሯ የሰብአዊ መብት አቀንቃኝ እና የነፃነት ታጋይ መሆኗን የኖቤል ኮሚቴው መረጃ ያመላክታል።
ናርጌስ ኢራን ውስጥ ሰብአዊ መብት፣ ነፃነት እና ዴሞክራሲ እንዲከበር በምታደርገው ተጋድሎ ሽልማቱ እንደተበረከተላትም ነው የተነገረው።
ወጣቷ በሴቶች ላይ የሚደርሰው ጭቆና እንዲቆም የምታደርገውን ተጋድሎ ያደነቀው ኮሚቴው “የነፃነት ታጋይ” ነበረች ሲልም አሞካሽቷታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version