Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ እና ዩኒዶ የ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ዮሮ የድጋፍ ሥምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 25 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) የ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ሥምምነት ተፈራረሙ።

ድጋፉ ‘በልማት ምርቶች፣ አገልግሎቶች እና የግልና የመንግስት አጋርነት ወጣቶችን እና ሴቶችን መደገፍ’ በሚል ስያሜ ለሚተገበረው ፕሮጀክት ማስተግበሪያ የሚውል ነው ተብሏል።

ለፕሮጀክቱ ማስተግበሪያ የሚለው ገንዘብም በድርጅቱ በኩል ከጣሊያን መንግስት የሚመደብ በጀት መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል።

ፕሮጀክቱ መንግስት በስራ እድል ፈጠራ የተቋማትን አቅም በማጠናከር ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶችና ሴቶች ለማበረታታት የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።

ለሁለት አመታት የሚቆየው ይህ ፕሮጀክት በሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በኩል የሚተገበር ነው።

የድጋፍ ሥምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና የዩኒዶ ተወካይ እና ቀጠናዊ ዳይሬክተር ኦሬሊያ ፓትሪዢያ ካላብሮ ተፈራርመውታል።

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version