አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፌደሬሽን ምክር ቤት የማንነት፣ የአስተዳደር ወሰንና የሰላም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እየመከረ ነው፡፡
ኮሚቴው ነገ ከሚካሄደው የፌዴሬሽን ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ጊዜ 1ኛ መደበኛ ስብሰባ ጋር ተያያዥነት ባላቸው አጀንዳዎች ላይ ነው እየተወያየ የሚገኘው፡፡
በዚሁ መሠረት በውይይቱ ላይ የኮሚቴው ፀሐፊ ፍቅሬ አማን የ2016 በጀት ዓመት የቋሚ ኮሚቴውን ዕቅድ አቅርበዋል፡፡
በተጨማሪም የተለያዩ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ጉዳዮችን በበጀት ዓመቱ ለመስራት ኮሚቴው እየመከረ መሆኑን የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
ቋሚ ኮሚቴው አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ብሄረሰቦችን አስመልክቶ በተዘጋጀው የጥናት ሰነድ ላይ ከተወያየ በኋላ ሰነዱን ለምክር ቤት ይዞ ይቀርባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተመላክቷል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!