Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከደቡብ አፍሪካው ኢታማዦር ሹም ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 13 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከደቡብ አፍሪካው ኢታማዦር ሹም ጀነራል ሩድዛኒን ማፕዋንያ ጋር ተወያይተዋል።

የደቡብ አፍሪካው ኢታማዦር ሹም ጀነራል ሩድዛኒን ማፕዋንያ በኢትዮጵያ እና በደቡብ አፍሪካ ያለውን ወታደራዊ ግንኙነት እና ትብብር ለማጠናከር ከፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር ተነጋግረዋል።

ኢታማዦር ሹሙ 116ኛውን የሠራዊት ቀን በክብር ለመታደም አዲስ አበባ ከባለቤታቸው ጋር መግባታቸውን የመከላከያ ሰራዊት ገጽ መረጃ ያመላክታል።

Exit mobile version