Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያና አሜሪካን ግንኙነትን ለማጠናከር ለሚከናወኑ ሥራዎች ድጋፍ ይደረጋል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ጄ. ማሲንጋን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በውይይታቸውም÷ በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በይበልጥ ለማጠናከር ለሚከናወኑ ሥራዎችም አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ እንደሚደረግ አቶ ደመቀ አረጋግጠዋል፡፡

አምባሳደር ማሲንጋ በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ ትብብር ዐቅሟን ለማውጣትና ለማሣደግ እንደሚያግዛት አመላክተዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version