Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የቤንቶኒቴ ማእድን ማውጫ እና ማምረቻን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፋር ክልል ዋርሰሶ ወረዳ የቤንቶኒቴ ማእድን ማውጫ እና ማምረቻን ጎብኝተዋል::

ቤንቶኒቴ ለሴራሚክ እና ቀለም ብሎም ለመሰል ምርቶች ጠቀሜታ በመዋሉ “ትንግርታዊ ርጥብ አፈር” እና “ብዝሃ ጥቅም ያለው ሸክላ አፈር” በመባል በአድናቆት የሚነሳ ሃብት መሆኑ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በአፋር ክልል የተለያዩ የልማት ሥራዎችን በመጎብኘት ላይ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version