Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አቶ አወል አርባ በአዋሽ ፈንታሌ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸውም በአካባቢው እየለማ የሚገኘውን የፓፓዬ ምርት እና ሌሎች ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡

አቶ አወል በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት÷ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡

ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት የሚደረገው ጥረት አበረታች እንደሆነም በማህበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version