👉ኢትዮጵያ ውስጥ የኑሮ ውድነት አለ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎች በኑሮ ውድነት ምክንያት ለመመገብ ይቸገራሉ ይሄ ጥያቄ እውነት ነው፡፡
👉ኢትዮጵያ ውስጥ ሳይሆን እዚሁ ከእኛ ቢሮ በመቶ ሜትር ርቀት ሰዎች ይቸገራሉ፤ ባለፉት 40 አመታት ያልታየ የዋጋ ግሽበት በዓለም ላይ አለ፤ የኢትዮጵያ ችግር ብቻ ሳይሆን የዓለም ችግር ነው፡፡
👉የኢትዮጵያን ያባባሰው የዋጋ ግሽበቱ የገቢ አቅማችን ዝቅተኛ በሆነበት ሁኔታና ላለፉት በርካታ አመታት ሳይቋረጥ እያደገ ስለመጣ የሰው ገቢና የግሽበት እድገት ምጣኔ በከፍተኛ ደረጃ ኑሮ ላይ ጫና አምጥቷል፡፡
👉ዋናው ችግራችንና ልንሰራበት የሚገባው ጉዳይ ግሽበት ነው ብለን ነበር፤ አንዳንድ ጊዜ ግሽበትንና የኑሮ ውድነትን አንድ አድርገን እናያለን፤
👉የኑሮ ውድነት የሚፈጠረው በዋጋ ግሽበት አደለም፤ ግሽበት እያለ ኑሮ ውድ ላይሆን ይችላል፤
👉የእኛ ችግር የሆነው ገቢያችን እያደገ ስለማይሄድ ነው፡፡
👉ዘንድሮ ያለው ሁኔታ ግን አጠቃላይ የዓለም የዋጋ ሁኔታ መረጋጋት እያሳየ እንደሚቀጥል ይተነበያል፤
👉በፋይናንስ ተቋማት የሚተነበየው ይረጋጋል የሚል ነው፤ የእኛንም ብትወስዱ አምና ስንነጋገር 37 በመቶ ነበር፤ በዚህ አመት መስከረም ላይ 28 በመቶ ወርዷል፤
👉ይህንን ጉዳይ ያወሳሰበው ነገር የእኛ የተደመረ ችግር ብቻ ሳይሆን ያደጉ ሀገራት የወሰዱት እርምጃ ጭምር ነው፤
👉ፈተናን አናስቀረውም፤ አንፈልግህምና አትምጣብን አንለውም፤ ነገር ግን ፈተና ስለሚለያይ እንደ አግባቡ ተገንዝቦ መወጣት ብቻ ነው ያለው መፍትሔ፤
👉ለዘመኑ ፈተና ራስን ማዘጋጀት፤ ፈተናውን እያለፍን እያሸነፍን የምንሄድበትን መንገድ መፍጠር ያስፈልጋል፤
👉ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እንዳይጎዱ ምርታማነት ማሳደግ፤
👉የኢትዮጵያ አርሶ አደር ግብር አይከፍልም፤ ግብር ለማይከፍል አርሶ አደር ድጎሞ የሚሰጥበት ዋናው ምክንያት ምርትና ምርታማነት ካደገ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ሰዎች ኑሮን በተዘዋዋሪ ይደጉማል በሚል እሳቤ ነው፡፡
👉ማዳበሪያ፣ ስኳር፣ ዘይትና ነዳጅ እንደጉማለን፤ የተማሪዎች ምገባና የቤት እድሳትም አለ፤
👉አዲስ አበባ ውስጥ አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ መሸጥ እንዲችል የገበያ ማዕከላት እየተገነቡ ይገኛሉ፤
👉አዲስ አበባ ላይ መሰራት የሚያስፈልገው ጉዳይ የቤት ኪራይ ጉዳይ ነው፤
👉የቤት ኪራይ በትክክል ህግ አውጥተን የማንገራው ከሆነ ሰው በየወሩ የቤት ኪራይ እየጨመረ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች ላይ ችግር እያመጣ ነው፡፡ ይሄን ማስተካከል ይኖርብናል፡፡
👉ዘንድሮ የሩዝ ምርት ላይ በክረምቱም በበጋውም በስፋት ተሰርቷል፡፡ 1 ሚሊየን ሄክታር ገደማ ታርሷል።
👉ከ40 ሚሊየን ኩንታል በላይ የሩዝ ምርትም እንጠብቃለን፡
👉የዕዳ ክፍያ በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል፡፡
👉ቡና አስፈላጊ እና የገቢ ምንጫችንም ስለሆነ በዓለም ገበያ ስርዓት ውስጥም በቀላሉ የተላመድነው ሸቀጥ ስለሆነ እንዲበላሽ መደረግ የለበትም፡፡
👉ፈተናዎች ግን አሉበት፤ በቡና የነበረውን ችግር እያሻሻሉ መሄድ ያስፈልጋል፤
በየሻምበል ምሕረት