Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አቶ በላይነህ ክንዴ ለለሚ እንጀራ ፋብሪካ ሶስት ተሽከርካሪዎችን አበረከቱ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለሃብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ ለለሚ እንጀራ ፋብሪካ ሶስት መለስተኛ ተሽከርካሪዎችን ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ድጋፉን አቶ በላይነህ ክንዴ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስረክበዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች በዚህ ወቅት÷ ተሽከርካሪዎቹ የለሚ እንጀራ ፋብሪካ በሙሉ አቅሙ ማምረት እንዲችል እያደረገ ባለው ጥረት በተቋሙ የሚሰሩ እናቶችን ለማመላለስ እንደሚውሉ ተናግረዋል፡፡

አቶ በላይነህ ክንዴም ለዚህ ዓላማ ላደረጉት የመለስተኛ ተሽከርካሪዎች ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል፡

Exit mobile version