የሶማሊያ ፕሬዚዳንት አዲስ አበባ ገቡ Melaku Gedif 2 years ago አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሊያ ፕሬዚደንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በ37ኛው የአፍሪካ ኀብረት መደበኛ የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዚዳንቱ በጉባኤው ለመሳተፍ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በመራኦል ከድር