አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በነገው ዕለት በክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች ዘንድ የሚከበረው የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል የመተሳሰብና የመደጋገፍ ሊሆን ይገባል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ ገለጹ፡፡
አፈ-ጉባዔው የትንሳኤ በዓልን በማስመልከት የመልካም ምኞት መልዕክት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስተላልፈዋል፡፡
በመልዕክታቸውም÷ ለመላው የክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች በዓሉ የሰላም፣ የመተሳሰብ፣ የፍቅር፣ የይቅርታ፣ የደስታ እና የአብሮነት እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡