Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የትንሳዔ በዓል የመተሳሰብ ሊሆን ይገባል- አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በነገው ዕለት በክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች ዘንድ የሚከበረው የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል የመተሳሰብና የመደጋገፍ ሊሆን ይገባል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ ገለጹ፡፡

አፈ-ጉባዔው የትንሳኤ በዓልን በማስመልከት የመልካም ምኞት መልዕክት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስተላልፈዋል፡፡

በመልዕክታቸውም÷ ለመላው የክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች በዓሉ የሰላም፣ የመተሳሰብ፣ የፍቅር፣ የይቅርታ፣ የደስታ እና የአብሮነት እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡

Exit mobile version