Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ያስገነባቸውን ቤቶች አስተላለፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን በኮየ ፈጬ እና በቃሊቲ ሳይቶች ያስገነባቸውን መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚዎች አስተላለፈ።

በቤቶቹ ማስተላለፍ በስነ-ስርዓት ላይ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ቤቶቹ በመከላከያ ኢንጂነሪንግ እና ኦቪድ ኮንስትራክሽን አማካኝነት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተገንብተው የተጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።

በመራኦል ከድር

Exit mobile version