Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ምስጋኑ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፈን አወር ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች እንዲሁም በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡

አምባሳደር ምስጋኑ÷በኢትዮጵያና ጀርመን መካከል ያለው ዘርፈ ብዙ ግንኙት እንዲጎለበት አምባሳደር ስቴፈን አወር  ላበረከቱት አስተዋጽኦ ማመስገናቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመልክቷል፡፡

Exit mobile version