Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አቶ አሕመድ ሽዴ ከጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) የተላከን መልዕክት ለኳታሩ አሚር አደረሱ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተላከን መልዕክት ለኳታሩ አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል ታኒ አድርሰዋል፡፡

አቶ አሕመድ ሽዴ ከኳታር አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል ታኒ ጋር በዛሬው ዕለት ተወያይተዋል፡፡

በውይይቱ ወቅትም አቶ አሕመድ ሽዴ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተላከን መልዕክት ለኳታሩ አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል ታኒ ጋር አስረክበዋል፡፡

መልዕክቱ የኢትዮጵያ እና ኳታርን የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዲሁም ሀገራቱ በቀጣይ ትብብራቸውን ማሻሻል የሚችሉባቸውን መንገዶች የሚያትት መሆኑ ተመላክቷል፡፡

Exit mobile version