Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በኮንሶ ዞን ከ29 ሚሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ሕገ-ወጥ የወባ መድኃኒቶች ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ) በተካሄደ ኦፕሬሽን በኮንሶ ዞን 29 ሚሊየን 172 ሺህ ብር ዋጋ ያላቸው ሕገ-ወጥ የወባ መድኃኒቶች መያዙን የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

ባለስልጣኑን ጨምሮ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የክልልና የፌዴራል ፖሊስ በጋራ በኮንሶ፣ ጅማ እና አዲስ አበባ ባካሄዱት ኦፕሬሽን የተለያዩ ሕገ-ወጥ የወባ መድኃኒቶች መያዛቸው ተገልጿል፡፡

በዚህም በኮንሶ ብቻ 29 ሚሊየን 172 ሺህ ብር የሚያወጡ የወባ መድኃኒቶች መያዛቸውን የባለስልጣኑ መረጃ አመላክቷል፡፡

ኦፕሬሽኑ በተለያዩ አካባቢዎች ተጠናክሮ መቀጠሉንም ነው የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ያስታወቀው፡፡

Exit mobile version