አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው የመመለስ ስራ መቀጠሉን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
በዚህ መሰረትም ከሕዳር 4 እስከ ሕዳር 27 ቀን 2017 ድረስ 1 ሺህ 155 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተጠቁሟል፡፡
ተመላሾቹ 446 ወንዶች፣ 631 ሴቶች እና 78 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ÷ ከእነዚህ መካከልም 218 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍና እንክብካቤ የማድረግና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
ከሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ከሳዑዲ ዓረቢያ ዜጎችን የመመለስ ሥራ እስካሁን ከ87 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ መመለስ መቻሉ ተጠቅሷል፡፡