Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በድሬዳዋ የመደመር ትውልድ ቤተ-መፃህፍት ግንባታ 50 በመቶ ደረሰ

 

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በድሬዳዋ ከተማ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቭ እየተገነባ ያለዉ የመደመር ትውልድ ቤተ-መፃህፍት ግንባታ 50 በመቶ መድረሱ ተገለፀ።

ቤተ መፃህፍቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተፃፈው የመደመር ትውልድ መፅሃፍ ሽያጭ ገቢ እየተገነባ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ የተመራ ልዑክ የቤተ መፃፍቱን የግንባታ ሂደት የጎበኘ ሲሆን÷ በዚህ ወቅት የግንባታው 50 በመቶ መጠናቀቁ መገለፁን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

ቤተ-መፃህፍቱ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ፣ የመፃህፍት መደብርና መሸጫ፣ ካፌና ሬስቶራንት ማካተቱ ታውቋል፡፡

 

Exit mobile version