Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአፈር መደርመስ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጉጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች በአፈር መደርመስ አደጋ ሕይወታቸው አለፈ፡፡

አደጋው ትናንት 9 ሰዓት በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ሥራ በተሰማሩ ዜጎች ላይ መድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አሸናፊ ዳንቆ ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

በአደጋው ለሕልፈት የተዳረጉ ሰዎችን አስከሬን ከተደረመሰው አፈር ውስጥ የማውጣት ሥራ መከናወኑንም አንስተዋል፡፡

በደበላ ታደሰ

Exit mobile version