Fana: At a Speed of Life!

በአፈር መደርመስ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጉጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች በአፈር መደርመስ አደጋ ሕይወታቸው አለፈ፡፡

አደጋው ትናንት 9 ሰዓት በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ሥራ በተሰማሩ ዜጎች ላይ መድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አሸናፊ ዳንቆ ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

በአደጋው ለሕልፈት የተዳረጉ ሰዎችን አስከሬን ከተደረመሰው አፈር ውስጥ የማውጣት ሥራ መከናወኑንም አንስተዋል፡፡

በደበላ ታደሰ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.