አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) መሬት ባንክ የገባ መሬትን በመውረር በተከናወነ ግንባታ ላይ ርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 2 መሬት ባንክ የገባን 1ሺህ ካ.ሜ መሬት ሁለት ግለሰቦች በሕገወጥ መንገድ የ2012 ዓ.ም ካርታ አለን በሚል የግንባታ ፍቃድ በማውጣትና ቦታውን በማጠር ግንባታ ለማከናወን ሲሞክሩ መያዛቸው ተገልጿል፡፡
የተከናወነውን ሕገ-ወጥ ግንባታ ማፍረሱን የገለጸው ባለስልጣኑ÷ጥፋተኞችን በሊዝ አዋጁ ተጠያቂ ለማድረግ በሒደት ላይ መሆኑን ጠቁሟል፡፡
በሕገ-ወጦች ላይ የሚወስደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ማስገንዘቡን የባለስልጣኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
የከተማዋ ነዋሪዎች ደንብ የሚተላለፉ ግለሠቦችን በ9995 ነፃ የስልክ መስመር በመደወል ጥቆማ እንዲሰጡም ጥሪ አቅርቧል።