Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ባህር ዳር ከተማ ኢትዮጵያ መድንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ባህር ዳር ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

ቀን 10:00 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ሰው ሰራሽ ሜዳ በተካሄደው ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ ሙጂብ ቃሲም እና ሔኖክ ይበልጣል ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።

ኢትዮጵያ መድህን ከሽንፈት ያልታደገውን ግብ ረመዳን የሱፍ አስቆጥሯል።

Exit mobile version