Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በከተሞች ዘመኑን የዋጀ የንጹሕ መጠጥ ውሃ አገልግሎት እንዲኖር እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በከተሞች ዘመኑን የዋጀ የንጹሕ መጠጥ ውሃ አገልግሎት እንዲኖር በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፡፡

የክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ውሃ ቢሮዎች እንዲሁም የከተሞች ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት አመራሮች የንጹሕ መጠጥ ውሃን ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እየመከሩ ነው፡፡

በሚኒስቴሩ የመጠጥ ውሃ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታምሩ ገደፋ በዚህ ወቅት ÷ በሀገር አቀፍ ደረጃ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በመድረኩ ከተሞች አሰራርን ይበልጥ በማዘመን ለደንበኞች ምቹና ቀልጣፋ የውሃ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የንጹህ መጠጥ ውሃን ባልተቆራረጠ መልኩ በከተሞች ተደራሽ ለማድረግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የኢትዮጵያ ከተሞች ውሃና ሳኒቴሽን ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ሙክታር አህመድ ናቸው።

በዚህ ረገድ የአዲስ አበባ እና አዳማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎቶች ለሌሎች አረአያ የሚሆኑ ሥራዎች መስራታቸውን አንስተዋል፡፡

በቀጣይ በከተሞች የሚስተዋለውን የውሃ አገልግሎት መቆራረጥ በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚሰራም አመልክተዋል፡፡

በጎህ ንጉሱ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

 

Exit mobile version