Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ በአስደናቂ የሕዳሴ ጉዞ ላይ ናት – የናይጄሪያ ም/ፕሬዚዳንት ካሺም ሼቲማ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በአስደናቂ የሕዳሴ ጉዞ ላይ ትገኛለች አሉ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዚዳንት ካሺም ሼቲማ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከናይጄሪያ ም/ፕሬዚዳንት ካሺም ሼቲማ ጋር ቁልፍ በሆኑ የሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ይታወቃል።

ምክትል ፕሬዚዳንቱ የኢትዮጵያን አስደናቂ ቅርሶችና ታሪኳን አጉልቶ በሚያሳይ መልኩ ታድሶ ለዕይታ ክፍት የሆነውን ብሔራዊ ቤተ መንግሥትንም ጎብኝተዋል።

ጉብኝታቸውን በተመለከተ በይፋዊ የክብር መዝገብ ላይ ባሰፈሩት የማስታወሻ መልዕክት ብሔራዊ ቤተ መንግሥቱ ህያው ታሪክ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ ሀገር መሆኗን ያወሱት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ፥ በአስደናቂ የሕዳሴ ጉዞ ላይ ትገኛለች ነው ያሉት።

በኢትዮጵያ ድንቅ የታሪክ ጸጋና ታላቅ ሀገርነት ኩራት እንደተሰማቸው መግለጻቸውንም ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

YouTube (http://www.youtube.com/@fanamediacorporation)

Exit mobile version