Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁሉም በባለቤትነት የሚሳተፍበት ነው – አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁሉም ዜጋ ሀገር ለመለወጥ በባለቤትነት የሚሳተፍበት የትውልድ አሻራ ነው አሉ፡፡

በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማን እና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ልማት ጋር የተሳሰረ ነው።

የአየር ንብረት ለውጥ በምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳለው ጠቁመው፤ ከዚህ አኳያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካባቢን ከመለወጥ ባሻገር ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማንሰራራት ትልቅ ሚና እንዳለው አብራርተዋል።

የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁሉም ዜጋ ሀገር ለመለወጥ በባለቤትነት የሚሳተፍበት የትውልድ ስራ መሆኑንም ተናግረዋል።

ሁሉም ዜጋ እጅ ለእጅ ተያይዞ በጋራ ከሰራ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ እንደምትለወጥ ጠቁመው፤ የተጀመሩ ስራዎችን በትብብር ማስቀጠል ይገባል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

“በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ 7 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞች ይተከላሉ።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version