Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ቤተክርስቲያኗ ከምክክር ኮሚሽን ጎን በመሆን ድጋፏን አጠናክራ ትቀጥላለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጎን በመሆን ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋገጠች።

የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ አቶ ጥበቡ ታደሰ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዛሬው ዕለት የምክክር አጀንዳዎቿን ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክባለች።

የቤተክርስቲያኗን አጀንዳዎች የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ ከሌሎች ብጹዓን አባቶች ጋር በመሆን ነው ያስረከቡት።

ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) በዚሁ ወቅት÷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምክክር ሂደቱ ከፍተኛ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን አንስተዋል።

ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ በበኩላቸው÷ በምክክሩ ሂደት ላይ ቤተክርስቲያኗ የነበራት ቅሬታ ተቀርፎ በአግባቡ እየተሳተፍን ነው ብለዋል።

ኮሚሽኑ ሀገርን የሚያሻግር ሥራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸው÷ በሁሉም የምክክር ሂደት እርከኖች እንድንሳተፍ እንዲሁም አጀንዳዎቻችንን በዚህ መልኩ አደራጅተን እንድናቀርብ እድል ስለሰጠን በቤተክርስቲያኗ ስም እናመሰግናለን ሲሉም ገልጸዋል፡፡

የቤተክርስቲያኗ አጀንዳዎች ለሀገርና ለሕዝብ ሰላም መረጋገጥ ጉልህ ሚና እናዳላቸው የገለጹት ብፁዕ አቡነ ፍሊጶስ የተጀመረውን ሰላም የማረጋገጥ ጉዞ እንዲሳካ ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን ድጋፏን አጠናክራ ትቀጥላለች ማለታቸውን አቶ ጥበቡ ተናግረዋል።

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version