Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በልዩ ድምቀት ይከበራል – አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በልዩ ድምቀት ይከበራል አሉ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር።

20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀንን በተመለከተ አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በተገኙበት የዐቢይ ኮሚቴ አባላት የመጀመሪያውን የመሪ ዕቅድ ውይይት እያካሄደ ነው።

አፈ ጉባኤ አገኘሁ በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ 20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚከበር መሆኑ የለውጡ መንግስት ጥያቄን የመመለስ ተግባራዊ ትሩፋትን የሚያሳይ ነው።

ቀኑ በልዩ ድምቀት እንደሚከበር አንስተው÷ ለዓመታት በልሂቃን መካከል ሲስተናገድ የነበረው ከፍተኛ የልዩነት ችግር ለመፍታት እንደ ሀገር ምክክር የሚደረግበት መሆኑን ጠቁመዋል።

በመድረኩ የሁሉም ክልል አፈጉባኤዎች፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች፣ ሚኒስትሮችና ሚኒስትር ዴኤታዎች ተገኝተዋል፡፡

20ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ኅዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ይከበራል።

በይስማው አደራው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version