Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በክልሉ ከ120 ሺህ በላይ ተማሪዎች በምገባ መርሐ ግብር ይካተታሉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን ከ120 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በምገባ መርሐ ግብር ለማካተት ዝግጅት ተደርጓል አለ ።
‎የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ደስታ ገነሜ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ በክልሉ ተማሪዎችን በትምህርት ቤት ምገባ በማካተት የሚስተዋለውን የትምህርት ማቋረጥ ለማስቀረት እየተሰራ ነው፡፡።
ባለፈው የትምህርት ዘመን በክልሉ ከ44ሺ በላይ ተማሪዎችን በምገባ መርሐ ግብሩ ማካተት መቻሉን አስታውሰው፥ ምገባው ተግባራዊ ከተደረገ ወዲህ በመማር ማስተማር ላይ መሻሻሎች መኖራቸውን ነው የገለጹት፡፡
‎በምገባ ሂደቱ የሚስተዋሉ ክፈተቶችን መገምገሙን ያነሱት ኃላፊው፥ ህብረተሰቡ በዚህ የትውልድ አደራ መሳተፉን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በሲሳይ ለገሰ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version