Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ሀገር አቀፍ የመጅሊስ ምርጫ ነገ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2017 ሀገር አቀፍ የመጅሊስ ምርጫ ነገ ይጀመራል አለ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ።
የምርጫ አሥፈጻሚ ቦርዱ ሰብሳቢ አብዱላዚዝ ኢብራሂም (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ ÷ ለሀገር አቀፍ መጅሊስ ምርጫ የመራጮች ምዝገባና ሌሎች የቅድመ ምርጫ ሥራዎች ተጠናቅቀዋል፡፡
አሁን ላይ የምርጫ ዝግጅት ምዕራፉን በማጠናቀቅ ወደ ምርጫ መሸጋገሩንም አመልክተዋል፡፡
በዚህ መሰረትም ምርጫው ከነገ ነሐሴ 9 ጀምሮ እስከ እሑድ ነሐሴ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚካሄድ ነው የገለጹት፡፡
በነገው ዕለት የዑለማዎች ምርጫ የሚከናወን ሲሆን÷ በቀጣይ ነሐሴ 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ.ም ደግሞ የምሁራን፣ የወጣቶች፣ የሴቶችና የሠራተኛውን ማሕበረሰብ ለሚወክሉ ተመራጮች ድምጽ ይሰጣል ብለዋል፡፡
ምርጫውን አሳታፊ፣ አካታችና ፍትሃዊ ለማድረግ በትኩረት መሰራቱን ጠቁመው ÷ ለምርጫው ከ13 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ መራጮች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ሙስሊሙ ማሕበረሰብ ለቀጣይ 5 ዓመታት ይወክለኛል የሚለውን ወኪል ካርድ ባወጣባቸው መስጅዶች በመገኘት ድምጽ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በጀማል አሕመድ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version