Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ 5 ጨዋታዎች ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ አምስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ፡፡

ትናንት የተጀመረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታዎች ዛሬ ቀጥለው ሲካሄዱ ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ አስቶን ቪላ ከኒውካስል ጋር ይገናኛል።

እንዲሁም ባለፈው የውድድር ዓመት በሊጉ ደካማ እንቅስቃሴ የነበረው ቶተንሃም 11 ሰዓት ላይ ዘንደሮ ወደ ሊጉ ካደገው በርንለይ ጋር ሲገናኙ÷ ብራይተን ከፉልሃም፣ ሰንደርላንድ ከዌስትሃም በተመሳሳይ ሰዓት ይጫወታሉ።

ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ደግሞ ወልቭስ ከፔፕ ጓርዲዎላው ማንቼስተር ሲቲ ጋር የሚያገናኘው ጨዋታ ተጠባቂ ነው።

በትናንትናው ዕለት በተጀመረው የሊጉ መጀመሪያ ጨዋታ ሊቨርፑል በርንማውዝን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version