አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2017 (ኤፍ ኤምሲ) የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ ማጠቃለያ መርሀ ግብር ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሚገኝበት በጉባ ተከናውኗል፡፡
የዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል ሲከናወን መቆየቱ ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ ማንሰራራት ማሳያ በሆነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተሳትፏል፡፡
በዘንድሮ ክረምት 714 ነጥብ 7 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀምበር መተከሉ ይታወሳል፡፡