Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ለ2018 ዓ.ም መስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው፤ የመስቀል በዓል እንደገና የመገለጥና እንደገና የማንሣት በዓል ነው ብለዋል።

መስቀሉ ከ300 ዓመታት በላይ ተቀብሮ የጠፋና የተረሳ፤ ያለቀና የደቀቀ መስሎ እንደ ነበር አንስተው፤ ከዘመናት በኋላ ግን ብርቱ መሪ ሲያገኝ ደመራው ተደምሮ፣ ተራራው ተቆፍሮ እንደገና በመውጣት ተገልጧል ብለዋል።

ይህ ለኢትዮጵያም የሚሠራ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ እንደገና ትነሣለች፣ እንደገና ታበራለች፣ እንደገናም ለዓለም ትገለጣለች ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version