Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከቻይና ፒፕልስ ባንክ ገዥ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከቻይና ፒፕልስ ባንክ ገዥ ፓን ኮንግሼንግ ጋር ከዓለም ባንክና ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ዓመታዊ ጉባኤ ጎን ለጎን ተወያይተዋል።

በውይይታቸው የኢትዮ ቻይና የፋይናንስ ትብብር በሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ የመከሩ ሲሆን፤ የድንበር ተሻጋሪ የንግድ ግንኙነት በሚጠናከርበት እና የዕዳ ሽግሽግ ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት አካሂደዋል።

የሁለቱ ሀገራት ማዕከላዊ ባንኮች እና የገንዘብ ተቋማት ንግድ እና የኢንቨስትመንት ፍሰትን እንዲያሳድጉ ለማስቻል ትብብራቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው ተነጋግረዋል።

ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የፋይናንስ ዘርፍን ጨምሮ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን ስትራተጂካዊ አጋርነት አጠናክራ ለማስቀጠል ያላትን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።

አጋርነቱ እየተከናወነ ከሚገኘው የኢኮኖሚ ሪፎርም ጋር በተናበበ መልኩ የሚከናወን መሆኑንም ተናግረዋል።

የሀገራቱን ዘላቂነት ያለው የጋራ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማስቀጠል የሚያስችል የቴክኒክ ውይይት እና ትብብር እንደሚቀጥል ሁለቱ ወገኖች ተስማምተዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version