Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከፕሬዚዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶኻን ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቱርክ ፕሬዚዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶኻን ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በኢኮኖሚ፣ በባሕል ወዳጅነት ግንኙነት፣ በዘላቂ ልማት እና የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራዎችን በሚያካትቱ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል፡፡

ውይይቱ በጆሃንስበርግ እየተካሄደ ከሚገኘው የቡድን 20 የመሪዎች ጉባዔ ጎን ለጎን ነው የተከናወነው፡፡

Exit mobile version