Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኢጋድ ዋና ጸኃፊ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን ለምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ጸኃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) አቅርበዋል።

ዋና ጸኃፊው ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት፤ ከአምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ጋር በቀጣናዊ እና ተቋማዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አድርገናል ብለዋል።

አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) የኢጋድን የጋራ አጀንዳ በመምራት ረገድ ትልቅ ሚና ወደሚጫወተው ስትራቴጂካዊ የፖሊሲ አካል ወደሆነው የኢጋድ አምባሳደሮች ኮሚቴ መቀላቀላቸውንም ዋና ጸኃፊው ገልጸዋል።

በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሾሙት ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን ሕዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version