Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ስታትስቲክስ ለጠንካራ ፖሊሲ የጀርባ አጥንት ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስታትስቲክስ መረጃን መሠረት ላደረገ ጠንካራ ፖሊሲ የጀርባ አጥንት ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ።

‎19ኛው የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት የብሔራዊ ስታትስቲክስ የዳይሬክቶሬት ጀነራል ኮሚቴ ዓመታዊ ስብሰባ ‘ፍትህና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካ’ በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

‎ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስብሰባው እንዳሉት፥ ‎ኢትዮጵያ ቀርጻ ወደ ትግበራ ያስገባቻቸው የልማት ግቦችና ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ተዓማኒ መረጃ ይፈልጋሉ።‎

ተአማኒ ስታትስቲክስ እና ልማት ተነጣጥለው እንደማይታዩ ጠቅሰው፥ ‎ስታትስቲክስ መረጃን መሠረት ላደረገ ጠንካራ ፖሊሲ እና ስትራቴጂ የጀርባ አጥንት ነው ብለዋል።

ውጥኖቹን ከግብ ለማድረስ የስታትስቲክስ ዘርፉ በሪፎርም ውስጥ ማለፉን ገልጸው፤ ዘርፉን በቴክኖሎጂ በማገዝ ኢትዮጵያ ጠንካራ ሥራ መስራቷን አመልክተዋል።

‎የዘርፉን ሚና ለማጎልበት ጠንካራ እና ገለልተኛ ተቋም መገንባት፣ ዘላቂ የፋይናንስ ምንጭ መፍጠር እና አኅጉራዊ ትስስርን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

‎እውነተኛ የስታትስቲክስ መረጃ እንደ ሀገር ሆነ እንደ አኅጉር የት እንደቆምን የማሳየት አቅም አለው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ኢትዮጵያ ዘርፉን ማዕከል ላደረጉ አኅጉራዊ ትግበራዎች ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።
‌‎
‎በወንድሙ አዱኛ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version