አዲስ አበባ፣ ሕዳር 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደ ሌሎች የልማት ስራዎቻችን ሁሉ በአገልግሎት አሰጣጥም እምርታ ለማምጣት እየሰራን እንገኛለን አሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስትቲትዩት የለማ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባ ስርዓት ይፋ አድርጓል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ ከንቲባዋ እንዳሉት÷ ስርዓቱ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ከተማዋን የሚመጥን አገልግሎት በመስጠት የነዋሪውን እንግልት ያስቀራል።
ስርዓቱ አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ የሚያዘምን መሆኑን ገልጸው፤ ባለጉዳዮች የተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በመጠቀም ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል።
የግዴታ ፎርም መሙላትን የሚያስቀር፣ በኢምግሬሽን፣ በጤና፣ በፍርድ ቤት፣ በብሔራዊ መታወቂያ እና በሎሎችም በተቋማት መካከል ቅንጅት እና መናበብን እንደሚፈጥር ተናግረዋል።
የመታወቂያ አሰጣጥ ላይ ያለ ፋይሉ ባለቤት ይሁንታ መታወቂያ እንዳይሰጥ መቆጣጠር የሚያስችል እና ሌሎችም በርካታ ዝርዝር አገልግሎቶችን ማጣመሩንም ጠቁመዋል።
ስርዓቱ ብልሹ አሰራርን በመከላከልና ግልጽነትን በማምጣት ረገድ የጀመርነውን ሰፊ ስራ ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
ቴክኖሎጂውን በአጭር ጊዜ ላበለፀገው ለኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ምስጋና አቅርበዋል።
በጀማል አህመድ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook WMCC
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

