Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ግብርናን በግብዓትና መካናይዜሽን በማስደገፍ ውጤታማ ለማድረግ እየተሰራ ነው – አቶ አዲሱ አረጋ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀገሪቱ የግብርናውን ዘርፍ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ በበቂ ግብዓትና መካናይዜሽን በማስደገፍ እየተሰራ ነው አሉ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ።

የግብርና፣ የንግድና ቀጣናዊና ትስስር እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴሮች በጋራ በመሆን የስንዴ ምርትና የቅባት እህሎችን ለማሳደግ ያለመ የባለድርሻ አካላት ውይይት አካሂደዋል።

አቶ አዲሱ በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ እንደ ሀገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ተኪ ምርቶችን በማብዛት የኤክስፖርት አቅምን ለማሳደግ፣ ለኢንዱስትሪዎች በቂ ምርቶችን ለማቅረብ እና ሰፊ የስራ እድልን ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

በዚህም ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ስራዎች አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸው÷ በስንዴ ሰብል የሚሸፈነው መሬት ከ4 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር ወደ 8 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር ማሳደግ ተችሏል ነው ያሉት።

በተጨማሪም 165 ሚሊየን ኩንታል የነበረው የምርት ግኝት ወደ 290 ሚሊየን ኩንታል ማሳደግ መቻሉንና ለስንዴ ግዥ ይወጣ የነበረውን 1 ቢሊየን ዶላር ማስቀረት እንደተቻለ አመላክተዋል።

በቅባትና ጥራጥሬ ምርትም ውጤታማነትን ለማሳደግ በተከናወነ ስራ ከዘርፉ ይገኝ ከነበረው 16 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል ወደ 37 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

አሁን ላይ 20 በመቶ የሚሆነው የዘይት ምርት በሀገር ውስጥ እየተመረተ እንደሚገኝ አንስተው÷ ይህንን ለማሳደግና ወደ ውጭ ለመላክ የሚያስችል አቅም ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም የእሴት ሰንሰለቱን በማጠናከርና የገበያ ትስስርን በመፍጠር ፈተናዎቹን ለማስቀረት እየተሰራ መሆኑንና ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን አብራርተዋል።

በታምራት ደለሊ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version