Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ሊቨርፑል እና ቼልሲ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ16ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሊቨርፑል እና ቼልሲ ተጋጣሚዎቻቸውን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

ምሽት 12 ሰዓት በሊጉ ደካማ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው ሊቨርፑል ብራይተንን ባስተናገደበት ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የሊቨርፑል ማሸነፊያ ግቦችን ሁጎ ኤኪቲኬ ገና ጨዋታው እንደተጀመረ በመጀመሪያው ደቂቃና በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ ጋር ማገናኘት ችሏል።

በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገው የቼልሲ እና ኤቨርተን ጨዋታ በቼልሲ የ2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

የቼልሲን ማሸነፊያ ግቦች ኮል ፓልመር እና ማሎ ጉስቶ አስቆጥረዋል።

የሊጉ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ ምሽት 2 ሰዓት ከ30 በርንሌይ ከፉልሃም እንዲሁም አርሰናል ከወልቭስ ምሽት 5 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook WMCC

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast  YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version