Fana: At a Speed of Life!

ሊቨርፑል እና ቼልሲ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ16ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሊቨርፑል እና ቼልሲ ተጋጣሚዎቻቸውን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

ምሽት 12 ሰዓት በሊጉ ደካማ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው ሊቨርፑል ብራይተንን ባስተናገደበት ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የሊቨርፑል ማሸነፊያ ግቦችን ሁጎ ኤኪቲኬ ገና ጨዋታው እንደተጀመረ በመጀመሪያው ደቂቃና በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ ጋር ማገናኘት ችሏል።

በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገው የቼልሲ እና ኤቨርተን ጨዋታ በቼልሲ የ2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

የቼልሲን ማሸነፊያ ግቦች ኮል ፓልመር እና ማሎ ጉስቶ አስቆጥረዋል።

የሊጉ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ ምሽት 2 ሰዓት ከ30 በርንሌይ ከፉልሃም እንዲሁም አርሰናል ከወልቭስ ምሽት 5 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook WMCC

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast  YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.