Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር በኮፕ 32 ዝግጅት ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ እና ቡድናቸው ጋር በኮፕ 32 ዝግጅት ዙሪያ ተወያይተናል ብለዋል፡፡

በውይይቱም ኢትዮጵያና የአፍሪካ ህብረት አህጉሪቱን በሚገባ የሚወክል ኮፕ 32 ለማዘጋጀት እንዴት ተቀራርበው መስራት እንደሚችሉ መምከራቸውን ተናግረዋል፡፡

በማህሙድ አሊ ዩሱፍ መሪነት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ኮፕ 32ን የተሳካ ለማድረግ የኢትዮጵያ ቁልፍ አጋር ለመሆን ቁርጠኛ መሆኑን ተገንዝቤያለሁ ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version