Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በክልሉ 2 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ልማት ገብተዋል

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ባለፉት 5 ወራት ከ2 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ልማት ገብተዋል አለ የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ።

የቢሮው ምክትል ሃላፊና የኢንቨስትመንት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ከበደ እንዳሉት ÷ በክልሉ ያለውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ይበልጥ ለማነቃቃት በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

ባለፉት 5 ወራት 42 ባለሃብቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቁመው ÷ ወደ ሥራ ከገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች መካከል 34ቱ በግብርና ዘርፍ መሰማራታቸውን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም አምስቱ በአገልግሎት ዘርፍ እና ሦስቱ ደግሞ በኢንዱስትሪ ዘርፍ መሰማራታቸውን ነው ያስረዱት፡፡

በፕሮጀክቶቹ ከ35 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የሥራ እድልን መፍጠር መቻሉን አቶ ተስፋዬ አመላክተዋል።

የክልሉን ሰፊ የመልማት አቅም ለመጠቀም በተከናወነ ሥራ የኢንቨስትመንት ፍሰት እየጨመረ መምጣቱን አስገንዝበዋል፡፡

በሁሉም የኢንቨስትመንት ዘርፎች ክልሉን ለማልማት ከባለሃብቱ ጋር በትብብር እንደሚሰራ ጠቅሰው ÷ በተለይም በኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ አልሚዎች ቅድሚያ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

በቅድስት በርታ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version