Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ዲጂታል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሳካት…

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዲጂታል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባን ማሳለጥ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሳካት ጉልህ ሚና አለው አሉ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት፡፡

ዋና ዳይሬክተሯ እንዳሉት ÷ ዲጂታል የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የኢትዮጵያን የለውጥ ጉዞ ለማሳለጥ እና ዜጎችን በላቀ ደረጃ ለማገልገል የሚደረገውን ጥረት ያግዛል፡፡

የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ መረጃዎች ለዲጂታል የማንነት መታወቂያ ሥርዓት ግንባታና ለፖሊሲ ቀረጻ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም አስረድተዋል፡፡

የምዝገባ ሥርዓቱን በአግባቡ ለመወጣትና የተጀመሩ ጠንካራ ሥራዎችን ለማስቀጠል ባለድርሻዎች ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ሥራን በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በመታገዝ በስኬት ለማጠናቀቅ በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በጠንካራ ዲጂታላይዜሽን ሥርዓት የተደገፈ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ሥርዓት መዘርጋት ለአስተዳደር፣ ለፍትሕ፣ ለዕቅድና ለልማት የማይተካ ሚና አለው ነው ያሉት፡፡

የሀገርን ደህንነት ለማረጋገጥ እና የዜጎችን ዓለም አቀፋዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ ጉልህ አበርክቶ እንዳለው አስገንዝበዋል፡፡

አሁን ላይ ያለውን ከወረቀት ብዙ ያልራቀ አሰራር ሥር ነቀል በሆነ መልኩ ለመቀየርና የተቀናጀ ዘመናዊ የዲጂታል ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡

በቅርቡም በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የተዘጋጀው የመመዝገቢያ ሥርዓት በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ መደረጉን አስታውሰዋል፡፡

በቀጣይ በመላው ኢትዮጵያ ወጥነት ያለውን የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version