Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በስልክ ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ከጓደኛዬ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ለፈረንጆቹ 2026 አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞት በስልክ ተለዋውጠናል ብለዋል፡፡

በውይይታቸውም ኢትዮጵያና ፈረንሳይ ያላቸውን ሁለንተናዊ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ መረጃ ለመለዋወጥ እና በትብብር ለማስራት መስማማታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook WMCC
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version