አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምሁር ችግር ፈቺና መፍትሄ አሳሽ ነው አሉ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዩኒቨርሲቲው 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ “የምሁራን ሚና ለሀገራዊ ብልጽግና” በሚል ርዕስ የጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ምሁር በስሜታዊነት የሚነዳ ሰው አይደለም ብለዋል።
ሐሳብ አክባሪ እና አፍቃሪ፤ ጥልቅ አሰላሳይ እና ብዙ ጠያቂ፤ አንባቢ፣ ነቃሽና ተንታኝነት የምሁር መገለጫዎች እንደሆኑ አስገንዝበዋል።
እንዲሁም ችግር ፈቺና መፍትሄ አሳሽነት የምሁር መገለጫ መሆኑን በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

