Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ቅድመ መደበኛ ትምህርት የወደፊቱን የሰው ሃይል ያጠናክራል- የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሕጻናት ቅድመ መደበኛ ትምህርት ለኢትዮጵያ ቁልፍ በዘርፉ የተወሰደ የማስተካከያ ርምጃ ነው አለ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፡፡

ቅድመ መደበኛ ትምህርት ሕጻናት በትምህርታቸውና በሕይወታቸው ስኬታማ እንዲሆኑ የሚያስፈልጋቸውን ክህሎትና እውቀት በማስጨበጥ ለዘላቂ ትምህርትና ለግል ስኬታማነት መሰረት የሚጥል ነው፡፡

ጥራት ያለው የቅድመ መደበኛ ትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋፋት መምህራንን ለማሰልጠን፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ምቹ የመማሪያ አካባቢን ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ጽ/ቤቱ ጠቅሷል፡፡

ለዚህም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሺዎች የሚቆጠሩ የመዋዕለ ሕጻናት ት/ቤቶች እየተቋቋሙ እንደሚገኙ ነው ያመላከተው፡፡

ቅድመ መደበኛ ትምህርት አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው የማሕበረሰብ ክፍሎች ዘንድ በመድረስ እኩልነትን ያረጋግጣል ያለው ጽ/ቤቱ÷ ማሕበራዊና የአስተሳሰብ እድገትን እንደሚያፋጥን ገልጿል፡፡

ከዚህ ባለፈም የሕጻናት ቅድመ መደበኛ ትምህርት የወደፊቱን የሰው ሃይል እንደሚያጠናክር ተጠቁሟል፡፡

ኢትዮጵያ በእነዚህ የመጀመሪያዎቹ የሕጻናት እድገት ዓመታት ላይ ሃብት በማፍሰስ፣ በራሱ የሚተማመን፣ የበቃ፣ ንቁና ተራማጅ የሆነ ትውልድ በመፍጠር የረጅም ጊዜ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገትን እያሳለጠች እንደምትገኝ ተጠቅሷል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version