Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የማሌ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ‘ዶኦሞ’ በዓል እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማሌ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ‘ዶኦሞ’ በዓል በፓናል ውይይትና በባህላዊ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ሌሞጌንቶ ከተማ ‘የዶኦሞ ብስራት ለሀገራዊ አንድነትና ዕድገት’ በሚል መሪ ሀሳብ እየተከበረ በሚገኘው በዓል ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ፤ የማሌ ብሔረሰብ የራሱ ቋንቋ፣ ባህላዊ የቀን አቆጣጠር ቀመር እና የአምልኮ ሥርዓት አለው ብለዋል።

በየዓመቱ ጥር 1 ቀን (ባሬ ፔቴ) የሚከበረው የዘመን መለወጫ ‘ዶኦሞ’ የተገባደደው ዓመት በምስጋና የሚሸኝበት እና ለአዲሱ ዓመት በጸሎት አቀባበል የሚደረግበት የብስራት በዓል መሆኑን ተናግረዋል።

የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ በበኩላቸው፤ ዶኦሞ የአንድነት፣ የሰላም እና የወንድማማችነት ተምሳሌት መሆኑን ገልጸዋል።

በዓሉ የማሌ ብሔረሰብን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና መንፈሳዊ እሴቶችን ከፍ ለማድረግና ታሪካዊ ቅርሶችን ለትውልድ ለማስተዋወቅ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል።

ዶኦሞ ቂም ተይዞ የማይከበር በመሆኑ የተጣላ የሚታረቅበት የአንድነት እና የሰላም በዓል መሆኑን ማመልከታቸውን የዞኑ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል ገልጿል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version