Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ከሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች፡-

👉 ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ ሲሰራ የነበረው የኢኮኖሚ ሪፎርም የማክሮ ኢኮኖሚ ስብራትን ለመቅረፍ ነው

👉 ግብርና መር መሆን ብቻውን የኢኮኖሚ ስብራታችንን ስለማይጠግን ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ በመከተል ጥራት ያለው ዕድገት ለመፍጠር ተሰርቷል፤

👉 ኢትዮጵያ ላለፉት 20 ዓመታት ጤነኛ ያልሆነ ብድር በመበደሯ እና ብድሩን መክፈል ባለመቻሏ ብድር መበደር የማትችል ሀገር ሆና ነበር፤

👉 ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢኮኖሚው ዘርፍ በኢትዮጵያ ታሪክ አመርቂ ውጤት የመጣበት ዘመን ነው፤

👉 አሁን ያለው የኢትዮጵያ ዕድገት ማንንም የሚያከራክር አይደለም፤

👉 የዛሬው ድህነት እኛ ላይ ሳያበቃ ወደ ልጆቻችን እንዳይሸጋገር መስራት አለብን፤

👉 በዓለም አቀፍ ግመታ በ2050 የዓለም ሕዝብ 9 ነጥብ 8 ቢሊየን ይደርሳል ተብሎ ይገመታል። ከዚህ ውስጥ 2 ነጥብ 5 ቢሊየን የአፍሪካ ሕዝብ ነው።

👉 የሕዝብ ቁጥር በስርዓት ከተመራ እና ከተገራ ለኢኮኖሚ እድገት አይተኬ ሚና አለው።

👉 በ2035 አፍሪካ ተጨማሪ 450 ሚሊየን ለስራ ዝግጁ የሆኑ ሰዎች ወደ ዓለም የስራ ገበያ ትቀላቅላለች፤ ከአሁኑ ጋር ሲደመር 1 ነጥብ 1 ቢሊየን ወጣት አፍሪካዊ ማልማት መስራት የሚችል ይሆናል።

👉 በዚህም ከዛሬ 10 ዓመት በኋላ ዓለም ለስራ ከሚፈልጋቸው ሰዎች መካከል 50 በመቶ የሚሆነው አፍሪካ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን÷ ይህንን በመረዳት ለነገ ውድድር ማዘጋጀት ይገባል።

👉 በሪፎርሙ ላይም ትውልድ ላይም አበክሮ መስራት ተችሏል።

በወንድማገኝ ፀጋዬ እና ዮናስ ጌትነት

Exit mobile version