Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ከሰጡት ምላሽና ማብራሪያ የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፡-

👉 በ2050 አብዛኛው የዓለም ሕዝብ ወደ ከተሜነት ይስፋፋል።

👉 በአዲስ አበባ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት አሁን ላይ በኢትዮጵያ በሚገኙ በርካታ ከተሞች ማስፋፋት ተችሏል።

👉 ይህ ስራ ከተሜነት እየተስፋፋ ሲሄድ ጤናማ ኑሮ የሚኖሩ፣ አካባቢያቸውን የሚወዱ፣ በሰላም ወጥተው የሚኖሩ እና በቂ አገልግሎት የሚያገኙ ዜጎች እንዲበራከቱ ያስችላል።

👉 እያደጉ ካሉ ሀገራት ከሀገር ውስጥ ምርታቸው ውስጥ ከ9 በመቶ ያላነሰ በአየር ንብረት ብክለት ችግር ምክንያት ጉዳት ያስተናግዳሉ።

👉 ይህ በልጆቻችን ላይ እንዳይደገም እና ተስማሚ ከባቢ እንዲፈጠር እየጠፋ ያለው አረንጓዴያማነት በአረንጓዴ ዐሻራ፤ እየተበላሸ ያለውን ወንዝ በወንዝ ዳር ልማት እየቀየርን እድገቱ ተፈጥሮን ሳያበላሽ ለማምጣት ሪፎርም ሲሰራ ነበር።

👉 በልጆች የትምህርት ሥርዓት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ቴክኖሎጂ፣ በአረንጓዴ ዐሻራ እና በከተሜነት በተሰሩ ስራዎች የመጣው ውጤት የሚታይ የሚጨበጥ ዓለም ዕውቅና የሰጠው ነው።

👉 ይህ ሁሉ ስራ ሲደመር የትናንት ስራ ሲደመር ልጆቻችን ቀና ብለው ከስደት ተቆጥበው በሀገራቸው በኩራት መኖር የሚችሉ ዜጎችን የማፍራት ትልም እና ፍላጎት በዕውቀት እና ዕቅድ ገብቶን እየሰራን እንዳለን ያመላክታል።

በዮናስ ጌትነት

Exit mobile version