አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት እያካሄደ ያለው መደበኛ ስብሰባ ቀጥሎ እየተካሄደ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው መደበኛ ስብሰባውን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት ስብሰባን ቀጥለናል ብለዋል።
የፓርቲው ምክር ቤት ባለፈው ሃሙስ ከሰዓት በኋላ በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት መደበኛ ስብሰባውን ማካሄድ መጀመሩ ይታወሳል።

